2013 ኦገስት 29, ሐሙስ

2013 ኦገስት 28, ረቡዕ

ያልተቀበልናቸው…(ክፍል 1)


ያልተቀበልናቸው…(ክፍል 1)

…ኢትዮጵያ ውስጥ እያሉ፤ ኢትዮጵያዊ እየሆኑ፤ እንደውጭ ዜጋ የምንቆጥራቸው አሉ፤ እንደ ውጭ ዜጋ ባንቆጥራቸውም ‹የእኛ ናቸው› ብለን አምነን ለመቀበል የምንቸገርባቸው አሉ - ከእነዚህ ብሄሮች ወይም ማህበረሰቦች ጋር አንድ ማዕድ አንቀርብም፤ ከብቶቻቸው ከከብቶቻችን ጋር አይውሉም፤ በጋብቻ ተዛምደን አጥንታቸው ከአጥንታችን ደማቸው ከደማችን ጋር አይዋሃድም፤ አልተቀበልናቸውም -ልክ እንደ መጻተኛ - ልክ እንደ ባይተዋር - ልክ እንደ ድንገተኛ እንግዳ - የሚታዩ ሆነዋል፡፡ ሀገሪቷ ከህጋዊ ባሏ ያልወለደቻቸው ይመስል ሳቅና ለቅሶዋን ከተቀሩት ልጆቿ እኩል የማይካፈሉ የሚመስለን፤ ውለታ የማያኖሩላትና ብድር የማይከፍሉላት የሚመስለን፡፡ ሳናውቃቸው፣ ሳንቀርባቸው፣ ሳንጠይቃቸው የሚያልፍ - ጥላ መስለው፣ ጥላ ለብሰው፡፡

2013 ኦገስት 27, ማክሰኞ

ሲጨልም



ወደ ሰባዎቹ የሚጠጉ የሚመስሉ አንድ አረጋዊ “ልጄ” አሉት አስተናጋጁን፡፡ “የወሰድኩትን መድኃኒት ይዤብህ መጣሁ፣ እባክህን የሰጠኸኝን ወስደህ . . .”
አላስጨርሳቸውም፡፡ ግርግዳው ላይ ወደተለጠፈው ጽሑፍ አመለከታቸው፡፡ ‘የተሸጠ መድኃኒት አይመለስም አረጋዊው’ በለሰለሱ ቃላት መማፀን ያዙ፡፡
“ሰውዬ ዞር በል! ስራ ልስራበት! ለእንቶ ፈንቶ ጉዳይ የማባክነው ጊዜ የለኝም. . .” አለ ቁጣው እየተወለደ፡፡
“ዛሬ በዚህ ሰውዬ እንድጨቀጨቅ ተፈርዶብኛል ልበል?”
“እባክህን ልጄ አሳፋሪ ነገር ደርሶብኝ ነው ዘመድና ዕድር የለለኝ በመሆኑ እንጂ . . . ” አሉ ትሁት በሆነች ፈገግታ ሊያባብሉት እየሞከሩ፡፡
“ቅናሽ ዋጋ ብትከፍለኝም . . .”
“ይሄ ሰውዬ ነካ ያረገዋል ልበል?” አለና ሌሎች መድኃኒት ገዥዎችን ያስተናግድ ገባ፡፡ “ከያዙ አይለቁ” 

2013 ኦገስት 24, ቅዳሜ

ብቻነት



ብቻነት
ልቤ ውስጥ ክረምት ገባ
የሀዘን ውሽንፍር
የብቻነት ዶፍ
ገላዬን አራሰው
      ወየው!
ልቤን!
ልቤን!!
ልቤን!!!
ነፍሴ ጎርፍ አትወድም
ነፍሴ ውርጭ አትለምድም
ጭጋግ ይጨንቀኛል
ብርሃን ይርበኛል…
ሰው የማታ ራቴ
ሰው የምኞት ጓዜ
ማን ይሆን ሳምራዊ
ማን ይሆን ቅን ወዳድ
እኔ ነኝ ባይ ማነው
የእግዜር አምባሳደር
ፀሃይን ሰርቆልኝ
ጨረቃዋን ጭምር
በልቡ ሙዳይ ውስጥ
ልቤን የሚያሳድር፡፡


ሰው ለሰው


አስናቀ- ‹ተወዳጁ› ሰይጣን

አበበ ባልቻ (አርቲስት) ‹ሰው ለሰው› የተሰኘውን ተከታታይ የቴሌቪዥን ድራማ ዝነኛ እንዲሆን አድርጐታል ብዬ አምናለሁ፤ ‹ሰው ለሰው› ድራማ  ከፍ ያለቦታ እንዲሰጠው አበበ ባልቻ ትልቅ ሚና ተጫውቷል ብዬም አምናለሁ፤ ረቡዕ በመጣ ቁጥር፤ መጥቶም በመሸ ቁጥር ሰዎች ማወቅ ከሚያጓጓቸው ነገሮች መካከል አንዱ ‹አስናቀ እንዴት እንደሰነበተ› መረጃ መለዋወጥ ሆኗል!
‹ሰው ለሰው› ውስጥ ያሉ ገጸ-ባህርያትና ድራማውን በመድረስ፣ በማዘጋጀት፣ በመተወንና ሙያዊ ድጋፍ በማድረግ እየተባበሩ ያሉ ሙያተኞች ስማቸውን በልባችን ውስጥ ማስፃፍ ችለዋል፤ በክብር እንግድነት የሚፈለጉባቸው መድረኮችም ጨምረዋል፤ በአጠቃላይ የ‹ሰው ለሰው›› ሰዎች የብዙዎቻችን ቤተኞች ሆነዋል፡፡ ይኼ መታደል ነው!! ግና ደራሲዎቹ (በተለይ ሰለሞን ዓለሙና መስፍን ጌታቸው) በየመጽሔቱ ስለዚህ ተከታታይ ድራማ በሚሰጡት ቃለ መጠይቅ ተባብሮ፣ ተከባብሮና የሚያጋጥሙ ችግሮችን በብልሃት እንዴት እንደሚወጡት ብናነብላቸውም፤ ድራማው ሊጠናቀቅ እየተቃረበ መሆኑንና ከዓመት በላይ እንደማይቆይ የሰጡትን መረጃ ልብ ብንለውም፤ እንደ ቴሌቪዥን ድራማው ተከታታዮች፤ እኔንና ጓደኞቼን ሲያሳስቡ የቆዩ ሶስት ነጥቦች አሉ፤ እነዚህ ነጥቦች ከወዲሁ ማረሚያ ካልተበጀላቸው፤ ማቃኛ ካልተደረገባቸው አንዳንድ ተመልካቾችን ድንዛዜ ውስጥ ሊከቱ ይችላሉ የሚል እምነት አለኝ፡፡
‹ሰው ለሰው› ውስጥ ያሉ ገጸ-ባህሪያትን ወክለው በመጫወት ብዙዎቹ የሚደነቁ ቢሆንም፤ ገጸ ባህርያቱን በመፍጠር በኩል ግን ደራሲዎች ልብ ያላሏቸው ወይም ችላ ብለው የናቋቸው ወይም በማጠቃለያ ክፍሉ ትኩረት ሰጥተን እንመለስባቸዋለን ብለው እስካሁን በቅጡ ሲዳስሷቸው ያላየናቸው ነጥቦች አሉ፤ እነሱም አንድ በድራማው ውስጥ ሴቶችን ደካማ አድርጐ መሳል፤ ሁለት፣ ተመልካቹ እንደ አርአያ የሚወስዳቸው ቤተሰቦች አለመኖር፤ ሦስት፣ ‹ሰይጣን› የሆነውን ገጸባህርይ አጀግኖ አሳዳጅ ፖሊሱን አኮስምኖ የማቅረብ ሁኔታ…

ስድብ አዘዋዋሪ ጽ/ቤት…



ስድብ አዘዋዋሪ ጽ/ቤት…

…ሰውየው ‹ያልተገባ ስድብ ተሰደብኩ!› ብሎ ተሳዳቢውን ሽማግሌ ፊት አቆመው አሉ፤ ሽማግሌውም የከሳሽና የተከሳሽን ‹ሙሉ ቃል› ካዳመጡ በኋላ፤ ተከሳሹን ይገስፁት ገቡ፤ ተከሳሽም ‹ስድቡ ከአንደበቴ በወጣ ጊዜ ጌሾና ብቅል አብረውኝ ነበሩ፤ ስካር ባይፀናወተኝ ኖሮ ከሳሼ ላይ ተዘባብቼ አንገቴን በሃፍረት ደፍቼ እፊትዎ አልቆምም ነበር!› የሚል ምላሽ ሰጠ፤ ከተሳዳቢው አንደበት የወጡት ስድቦች ተሰዳቢውን ከመግለጽ ይልቅ የሰዳቢውን ደረጃ እና ትክክለኛ ውስጣዊ መልክ የሚያሳይ መሆኑን ሽማግሌው ልብ አሉ! እናም ሁለቱን አስታርቀውና ፍርድ አደላድለው ከሰዳቢና ተሳዳቢ መሃል ሆነው መንገድ ሲቀጥሉ ያያቸው አንድ ሰው ‹አባቴ ከየት ነው?› ብሎ ጠየቃቸው፤ እሳቸውም ‹ስድብ አዘዋውሬ መጣሁ!› አሉ- አሉ ነው እንግዲህ!
…አሁን ባለንበት ዘመን ብዙ ስድቦች አሉ- አለቦታቸው የተነገሩ፤ አለመልካቸው የተገለፁ፤ አለውክልናቸው የተሰጡ፡፡ እነዚህ ስድቦች አንዳንዶቹ የት መጣነታቸው ይታወቃል፤ የፈለቁበት ምንጭ ይገመታል፡፡
ስድብ ከንቀት ማህፀን ብቻ አይደለም የሚወለደው፤ ስድብ ፍራቻ እና ጥላቻም አምጠው ይወልዱታል፡፡ የናቅነውንና በአካልም በመንፈስም እንዳይጠጋን የምንሸሸውን ብቻ አይደለም የምንሰድበው፤ ነገ ከነገ ወዲያ ጉዳት ያደርስብን ይሆናል፣ በእኔ ላይ የማዘዝ ስልጣን ይጐናፀፍ ይሆናል ብለን በስጋት የምንጠነቀቀውንም እንሰድበዋለን፡፡
በስድባችን አንገቱን እናስደፋዋለን፤ በስድባችን መጠጊያ ጥግ እናሳጣዋለን፤ በስድባችን ማረፊያ ጥላውን እናጥርበታለን፡፡

2013 ኦገስት 16, ዓርብ

የመኝታቤት ምስጢሮች


ከጥቁር ሰማይ ስር


ምጣዱ



ከርቀት  
አንድ ሰባኪ ድምጹን አስጩሆ የመዝጊያ ጸሎት ሲያካሂድ ይሰማታል፡፡
“የዕለት እንጀራችንን ስጠን ዛሬ . . .”
“አሜን” አለች - ፈገግ ብላ፡፡ አልጋዋን ዐየችው - የዕለት እንጀራዋን የምትጋግርበት ምጣዷን፡፡
አሁን የምትኖርበት ክፍል - ነፍሳቸውን ይማረውና - የእናቷ ነበር፡፡ እናቷ ከከፈላቸው  ሁሉ ይተኙበት የነበረው አልጋ አሁንም አለ፡፡ አሁንም የመክፈል አቅም ካላቸው ጋር ልጅቱ ትተኛበታለች፡፡ ልጅቱ በተረገዘችበት የሽቦ አልጋ ላይ ነው እንጀራዋን እየጋገረች ያለችው፡፡
ከመወለዷ አስቀድሞ በተገዛ መስታወት ዐይኖቿን ፈለገቻቸው፡፡ ዐይኖቿ ትናንሽ ስለሆኑ አጨንቁራ የምታይ ያስመስላታል፡፡ መልኳን ትክ ብላ እያየች፣ እናቷ በሕይወት ብትኖር ኖሮ ምን ልትመስል ትችል እንደነበር ማሰላሰል ያዘች፡፡
እናቷን ማሰብ ስትጀምርና ሆድ በሚያስብሱ ነገሮች ስትከበብ፤ መስታወት ፊት ትቆምና መልኳ ላይ አፍጥጣ ስትነጫነጭ ታመሻለች፡፡